በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው፡፡

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉባኤው ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚ ሆነዋል።

በገጠርና በከተማ የስራ ፈላጊዎችን በመለየትና በመመዝገብ ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለ379 ሺ 430 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን በሪፖርታቸው ጠቁመዋል።

በክልሉ ከ60 ሺ በላይ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩንም የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ከእነዚህ ውስጥ 39 ሺ 879 ወደ ቋሚ እንዲሸጋገሩ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ኢንተርፕራይዞች ተኪ ምርት እንዲያመርቱ በተደረገው ትኩረት 210 ያህሉ 5354 ቶን በማምረት 19 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ማዳን ስለመቻሉም ገልፀዋል።

በበጀት አመቱ 637 ሚሊዮን 210 ሺህ 422 ብር ብድር መሰራጨቱን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለኢንተርፕራይዞች ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን በላይ ብር የገበያ ትስስር ተፈጥሯል ብለዋል።

ዘጋቢ፡ መለሰች ዘለቀ