በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው፡፡
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉባኤው ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚ ሆነዋል።
በገጠርና በከተማ የስራ ፈላጊዎችን በመለየትና በመመዝገብ ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለ379 ሺ 430 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን በሪፖርታቸው ጠቁመዋል።
በክልሉ ከ60 ሺ በላይ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፈጠሩንም የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ከእነዚህ ውስጥ 39 ሺ 879 ወደ ቋሚ እንዲሸጋገሩ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ኢንተርፕራይዞች ተኪ ምርት እንዲያመርቱ በተደረገው ትኩረት 210 ያህሉ 5354 ቶን በማምረት 19 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ማዳን ስለመቻሉም ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ 637 ሚሊዮን 210 ሺህ 422 ብር ብድር መሰራጨቱን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለኢንተርፕራይዞች ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን በላይ ብር የገበያ ትስስር ተፈጥሯል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ መለሰች ዘለቀ

More Stories
ምክር ቤቱ በ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ
በበጀት አመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
በበጀት አመቱ በክልሉ ከ160 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ ተችሏል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)