በበጀት አመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በበጀት አመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሔደ ነው።
በበጀት አመቱ ከማዘጋጃ ቤታዊና ከመደበኛ ገቢ 26 ቢሊዮን 607 ሚሊዮን 38 ሺህ ብር መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።
አፈፃፀሙም ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ9 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለው ርዕሰ መስተዳደሩ በሪፖርታቸው ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ መለሰች ዘለቀ

More Stories
ምክር ቤቱ በ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ
በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
በበጀት አመቱ በክልሉ ከ160 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ ተችሏል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)