አርሰናል የብሩኖ ጊማራኤስን ዝውውር ለማጠናቀቅ ከስምምነት ደረሰ!
አርሰናል የኒውካስል ዩናይትድ እና የብራዚል ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ብሩኖ ጊማራኤስን በይፋ ለማስፈረም የሚያስችለውን የ80 ሚሊዮን ፓውንድ ስምምነት መፈጸሙን ዘ ሳንዴይ ታይምስ ዘግቧል።
የ28 ዓመቱ ብሩኖ ጊማራኤስ፣ በነገው ዕለት በለንደን ተገኝቶ የህክምና ምርመራ እንደሚያደርግ እና የአምስት ዓመት ኮንትራት እንደሚፈርም ተጠቅሷል።
ሚኬል አርቴታ የመሃል ሜዳ ክፍላቸውን የበለጠ ለማጠናከር እና በቀጣዩ የውድድር ዘመን ውስጥ ሊጎች እና በአውሮፓ መድረክ በጠንካራ ሁኔታ ለመፎካከር ብሩኖ ጊማራኤስን ቀዳሚ ኢላማቸው አድርገውት ቆይተዋል።
ጊማራኤስ ኳስ የመንጠቅ፣ ጨዋታ የመምራት እና ጥቃቶችን የመመስረት ከፍተኛ ብቃት ያለው በመሆኑ ለአርሰናል የመሃል ክፍል ትልቅ ተጨማሪ ኃይል ይሆናል ተብሎ ይገመታል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንችስተር ዩናይትድ ሉዊስ-ስኬሊን ለማስፈረም እንቅስቃሴ ጀምሯል
የቪኒሲየስ ጁኒየር እና ሪያል ማድሪድ ውጥረት፡ “ተቀበል ወይም ልቀቅ!”
ሪያል ማድሪድ ሮድሪ ለማስፈረም ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ አቀረበ!