የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጉራጌ ዞን አገና ከተማ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጉራጌ ዞን አገና ከተማ አስጀምረዋል፡፡
በጉራጌ ዞን በአገና ከተማ የአንዲት አረጋዊት ቤት በማፍረስ አዲስ የግንባታ ስራ ዶ/ር መሀመድ አስጀምረዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል እና የጉራጌ ዞን አመራሮች የተገኙ ሲሆን በአገና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የአረንጓዴ አሻራ አሳርፈዋል።
“በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መርህ በተከናወነው በዚህ ተግባር የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች እና የማህበረሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ምትኬ ገ/ወልድ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ ከፍተኛ የመንፈስ እርካታ የሚያጎናጽፍ ተግባር በመሆኑ ተግባሩን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ(ዶ/ር) ገለፁ
የክረምት ጊዜያቸውን ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ባላቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ ማዋላቸው ደስታ እንደፈጠረላቸው የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች ተናገሩ
ህብረተሰቡን ያሳተፈ የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተሰረው ስራ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡ ተገለጸ