የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጉራጌ ዞን አገና ከተማ ተጀመረ

የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጉራጌ ዞን አገና ከተማ ተጀመረ

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጉራጌ ዞን አገና ከተማ አስጀምረዋል፡፡

በጉራጌ ዞን በአገና ከተማ የአንዲት አረጋዊት ቤት በማፍረስ አዲስ የግንባታ ስራ ዶ/ር መሀመድ አስጀምረዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል እና የጉራጌ ዞን አመራሮች የተገኙ ሲሆን በአገና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የአረንጓዴ አሻራ አሳርፈዋል።

“በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መርህ በተከናወነው በዚህ ተግባር የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች እና የማህበረሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው።

ዘጋቢ፡ ምትኬ ገ/ወልድ – ከወልቂጤ ጣቢያችን