ክረምትና የበቆሎ እሸት
በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች በክረምት ወቅት የበቆሎ እሸት ጥብስ እና ቅቅል በየመንገድ ዳሩ ሲሸጥ ማየት የተለመደ ነው፡፡
በሀዋሳ ከተማም በክረምት ወቅት በየመንገድ ዳር የበቆሎ ጥብስ እና ቅቅል ገበያው ይደራል፡፡
ክረምትና እሸት የማይነጣጠሉ እስኪመስሉ ድረስ በተለይም አመሻሽ አካባቢ ሰዎች ከስራ ገበታቸው ሲወጡ፣ የማታ የእግር ተጓዦች( ወክ የሚበሉ ) እና ሌሎችም በአጋጣሚ በመንገዳቸው ሲያልፉ ያጋጠማቸው ሰዎች በየመንገዱ ሽታው የሚያውደው የበቆሎ ጥብስና ቅቅል በመግዛት የክረምቱን ቅዝቃዜ ያስታግሳሉ፡፡
ከዛም አልፎ እሸት በመግዛት ወደ ቤቱ ይዞ የሚሄድ ሰው ቁጥርም ብዙ ነው፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ በየጎዳናው በቆሎን በመጥበስና በመቀቀል ለገበያ የሚያውሉ ሰዎች ኑሯቸውን ለመደጎም እንደ ገቢ ምንጭ አማራጭ ይጠቀሙታል፡፡
በሀዋሳ ጎዳናዎች በቆሎ ሲሸጡ ያገኘናቸው ነጋዴዎችም በተለይም በዚህ በክረምት ወቅት ገበያው እንደሚደራ ገልጸው በቆሎ በእሸት፣ በጥብስና በቅቅል መልኩ አዘጋጅቶ በመሸጥ ተጠቃሚ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
አዘጋጅ ፡ ሰብለ ደምሴ

More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።