35 በመቶ የሚሆኑ ውሃ አዘል መሬቶች እየጠፉ መምጣታቸውን የተለያዩ ጥናቶች አመላካቱ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዓለም አቀፍ ደረጃ በተደረገው ጥናትና ምርምር 35 በመቶ የሚሆኑ ውሃ አዘል መሬቶች እየጠፉ መምጣታቸውን የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያመላከቱ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ገለጸ፡፡
በናቡ ኢትዮጵያና በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ አማካይነት በውሃ አዘል መሬቶች ዙሪያ የተደረገውን ዳሰሳ ጥናት ተከትሎ በቦንጋ ከተማ ሲካሄድ የነበረው ምክክር መድረክ ተጠናቋል፡፡
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ የተፈጥሮ ሀብት ትምህርት ክፍል መምህር እና የዳሰሳ ጥናቱ ቡድን መሪ ዶክተር አብይ ጌታቸው ውሃ አዘል መሬቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተመናመኑ መምጣታቸው በናቡ ኢትዮጵያ አስተባባሪነት በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ማረጋገጥ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ 35 በመቶ የሚሆኑ ውሃ አዘል መሬቶች መጥፋታቸው በጥናት መረጋገጡን ገልጸው፥ የውሃ አካላትን መጠበቅና መንከባከብ እንደሚገባ አሰገንዝበዋል፡፡
የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ግርማ ጥላሁን የቀረበው የዳሰሳ ጥናቱ ለሌሎች ምርምር ስራዎች ትልቅ ዕገዛ እንዳለው አንስተዋል፡፡
መድረኩ አስተዳደራዊ ዕቅድ ለማዘጋጀት መነሻ ሀሳብ የተገኘበት ስለመሆኑም ተመላክቷል፡፡
ከተሳታፊዎች መካከል የቤንች ሸኮ እና የካፋ ዞን ግብርና፣ ደን አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል፣ አቶ አክሊሉ አማዴና ሌሎችም እንደገለጹት ናቡ ኢትዮጵያ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመቀናጀት የሰራቸው ሥራዎችና የዳሰሳ ጥናቱ ያስገኘውን ተሞክሮ አጠናክሮ ማስቀጠልና ተግባራዊ ማድረግ ይገባል በማለት አስተያየታቸው ሰጥተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ብዙአየሁ ጫካ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የቤት ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
በሀገሪቱ የሚገኙ ውሃ አዘል መሬቶችንና ተፋሰሶችን የማልማት ተግባር በጥናት በማስደገፍ እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ
ከ16 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት በበልግ እርሻ በበቆሎ ማሳ ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ