የአብሮነት ምልዕክት

የአብሮነት ምልዕክት

‎ወ/ሮ ፋጡማ መቻል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ስትሆን የእስልምና ዕምነት ተከታይ ናት።

‎በነገው ዕለት በሀዋሳ በድምቀት የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ሀዋሳ ከተማ የመጡ እንግዶችን ስትቀበል አግኝተን ያነጋገርናት ሲሆን በዓሉን በአብሮነት በሰላም እንዲከበር ከሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ጋር በመሆን እንግዶችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብላ መቀበሏ ደስታ እንደፈጠረላት ትገልጻለች።

‎ሀዋሳ ከተማ ሁሉም ሀይማኖቶች በፍቅር፣ በመተሳሰብና በአንድነት የሚኖሩቧት ከተማ እንደሆነች ወ/ሮ ፋጡሟ የተናገረች ሲሆን ለመላው የክርስትና እምነቱ ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክትም አስተላልፋለች።

‎ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ