የአብሮነት ምልዕክት
ወ/ሮ ፋጡማ መቻል የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ስትሆን የእስልምና ዕምነት ተከታይ ናት።
በነገው ዕለት በሀዋሳ በድምቀት የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ሀዋሳ ከተማ የመጡ እንግዶችን ስትቀበል አግኝተን ያነጋገርናት ሲሆን በዓሉን በአብሮነት በሰላም እንዲከበር ከሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ጋር በመሆን እንግዶችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብላ መቀበሏ ደስታ እንደፈጠረላት ትገልጻለች።
ሀዋሳ ከተማ ሁሉም ሀይማኖቶች በፍቅር፣ በመተሳሰብና በአንድነት የሚኖሩቧት ከተማ እንደሆነች ወ/ሮ ፋጡሟ የተናገረች ሲሆን ለመላው የክርስትና እምነቱ ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክትም አስተላልፋለች።
ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ
የአብሮነት ምልዕክት

More Stories
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ
የቡታጅራ ግራንድ ቪው ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 164 ተማሪዎች ለ2ኛ ዙር አስመረቀ
ሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን መንስኤ በመለየት ችግር ፈቺ መፍትሄዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቆመ