የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የኦሞ ቱርካና ምርምር ጣቢያ ማቋቋሚያ የአጋር አካላት ግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል
በመድረኩ ከጂማ ዩኒቨርሲቲ ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከፌደራል ግብርና ሚኒስቴር፣ ከሠላም ሚኒስቴር፣ ከዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል፣ ከኢትዮጵያ እርሻ ምርምር፣ ከደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር እና ሌሎች መንግስታዊና መንስግታዊ ያልሆኑ አጋር አካላት እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኦሞና የቱርካና ሀይቅ እና በአካባቢው ላይ ትኩረቱን ያደረገ በዩኒቨርሲቲው ምሁራን የተደረገ ጥናትና ምርምር እየቀረበ ይገኛል።
በመጨረሻም ከተሳታፊ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ መድረኩ እንደሚጠናቀቅ የወጣው መርሀ-ግብር ያሳያል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳኛቸው ደሴ – ከጂንካ ጣቢያችን
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የኦሞ ቱርካና ምርምር ጣቢያ ማቋቋሚያ የአጋር አካላት ግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል

More Stories
በክልሉ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚሠራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
አሰልጣኞች ወቅቱ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲላበሱ እየተሠራ መሆኑ ተጠቆመ
በቴክኖሎጂ የተካኑ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት በመሥራት ሀገሪቱን ማበልጸግ እንደሚገባ ተገለጸ