የጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምስ ገብሬ አውደ ርዕዩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፥ በዞኑ ከ790 በላይ የፈጠራ ስራዎች ውድድር በተማሪዎች፣ በኢንተርፕራይዞች እና በመምህራን እንዲሁም በኮሌጆች እና በግል ተሰርተው ቀርበዋል።
የፈጠራ ስራዎች ምዘናው ሲካሄድ በተገቢው በመከታተልና በአግባቡ በማስመዘን ለውጤት ማብቃት ይጠበቃል ሲሉም አሳስበዋል።
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ መብራቴ ወልደማሪያም በበኩላቸው የፈጠራ ስራዎች ውድድሩ በትክክለኛ መንገድ በመመዘን ውጤታማ ተወዳዳሪዎች በክልል መድረክ እንዲሳተፉ እድል የሚፈጥር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል።
በዞኑ ካለፉት አራት አመታት ወዲህ በፈጠራ ስራዎች ውድድር አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ መብራቴ አሁንም ወቅቱ የሚፈልግውን የፈጠራ ስራ በመስራት እና በክልል ደረጃ ተፎካካሪ መሆን እንደሚገባም አመላክተዋል።
የፈጠራ ስራዎች ውድድሩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ እርካብነሽ ወልደማርቆስ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የዲጂታል ዘመን ኮሙኒኬሽን የመረጃ ስርጭት ብቻ ሳይሆን የሕዝብ እምነት የሚገነባበት እና የተቋማትን ገጽታ የሚያጠናክር መሆኑ ተገለጸ
ሀገራችን ኢትዮጵያ በእውቀት፣ በክህሎትና በስነ-ምግባር የበለፀገና የሰለጠነ የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለማፍራት በአዳዲስ ፈጠራና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ከ5ሺ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ በበይነ መረብና በወረቀት እያስፈተነ መሆኑን የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ገለፀ