የጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምስ ገብሬ አውደ ርዕዩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለፁት፥ በዞኑ ከ790 በላይ የፈጠራ ስራዎች ውድድር በተማሪዎች፣ በኢንተርፕራይዞች እና በመምህራን እንዲሁም በኮሌጆች እና በግል ተሰርተው ቀርበዋል።
የፈጠራ ስራዎች ምዘናው ሲካሄድ በተገቢው በመከታተልና በአግባቡ በማስመዘን ለውጤት ማብቃት ይጠበቃል ሲሉም አሳስበዋል።
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ መብራቴ ወልደማሪያም በበኩላቸው የፈጠራ ስራዎች ውድድሩ በትክክለኛ መንገድ በመመዘን ውጤታማ ተወዳዳሪዎች በክልል መድረክ እንዲሳተፉ እድል የሚፈጥር ነው ሲሉም አስገንዝበዋል።
በዞኑ ካለፉት አራት አመታት ወዲህ በፈጠራ ስራዎች ውድድር አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ መብራቴ አሁንም ወቅቱ የሚፈልግውን የፈጠራ ስራ በመስራት እና በክልል ደረጃ ተፎካካሪ መሆን እንደሚገባም አመላክተዋል።
የፈጠራ ስራዎች ውድድሩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ እርካብነሽ ወልደማርቆስ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የኦሞ ቱርካና ምርምር ጣቢያ ማቋቋሚያ የአጋር አካላት ግንዛቤ መፍጠሪያ ስልጠና በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል
በክልሉ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚሠራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
አሰልጣኞች ወቅቱ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲላበሱ እየተሠራ መሆኑ ተጠቆመ