የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል

የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል

የዙሪያ ወረዳው ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ካሳሁን ቆሶ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫና የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላን በስኬት ባጠናቀቀችበት ማግስት የሚካሄድ ጉባኤ መሆኑ ልዩ የሚያደርገው መሆኑን ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ ያለፈውን መደበኛ ቃለ ጉባኤ፣ ምክር ቤቱ በ2018 በጀት አፈጻጸም ዙሪያ ሐሳብ አስተያየት ሰጥቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

የምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ እንዲሁም ማስፈጸሚያ በጀት ለአባላቱ ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶበት በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተመሥገን አዘነ፤ የአስተዳደር ምክር ቤቱን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

ዋና አስተዳዳሪው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አይናለም መኮንን የፍርድ ቤቱን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም፣ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድና የ2019 በጀት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ምክር ቤቱ የዙሪያ ወረዳውን የፍርድ ቤት የ2019 በጀት 6 ሚሊዮን 967 ሺህ 519 ብር እንዲሆን አፅድቋል።

ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን