የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ አሳታፊ እና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የመሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጀንሲ Giz ከተሰኘ የጀርመን አለም አቀፍ የልማት ድርጅት ጋር በመተባበር በከምባታ ዞን በአንበርቾ ተራራ እና በጉራጌ ዞን በአረቅጥ ሀይቅ አሳታፊና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ዙሪያ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የህልውና መሠረት የሆነውን የመሬት ገጽታና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን የመጠበቅና መንከባከብ ኃላፊነት የማህበረሰቡ እና የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊሆን እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

በመድረኩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የመሬት አሰተዳደር እና አጠቃቀም ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አብዱልአፊዝ ሀሰን፣ የፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር እና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የጀርመን አለም አቀፍ የልማት ድርጅት አማካሪ አቶ አንተነህ ወንድሙ እና ተወካዮች እንዲሁም የማህበረሰብ ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ዘጋቢ፡ ኤርጡሜ ዳንኤል እና መልካሙ ታፈሰ – ከሆሳዕና ጣቢያችን