ብሔራዊ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የተሻለ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚጠቅም ተገለጸ‎

ብሔራዊ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የተሻለ አገልግሎት ለማግኘት እንደሚጠቅም ተገለጸ‎

‎በጌዴኦ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ብሔራዊ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ንቅናቄ መድረክ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።‎

‎ብሔራዊ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ከ5 ዓመት በላይ ዕድሜ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ሁሉ ወሳኝነት እንዳለው ተመላክቷል።‎‎

‎የንቅናቄ መድረኩን በውይይት የከፈቱት የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደሰ፤ ህዝቡን ለፋይዳ መታወቂያ ስንመዘግብ ቀድሞ መግባባትና ቅድመ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ይጠበቅብናል ብለዋል።‎

‎አክለውም ከማኑዋል ወደ ዲጂታል ሲስተም ለመቀየር በሚደረገው ጥረት ሁሉም የድርሻቸውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።‎

‎የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የጌዴኦ ዞን ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ሾንጣ፤ በሁሉም የአገልግሎት ዘርፍ ተጠቃሚ ለመሆን ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አስረድተዋል።‎

‎ለፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ኢትዮ ቴሌ፣ ፖስታ ቤትና የንግድ ባንክ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸውም አቶ ደረጀ አስገንዝበዋል።‎

‎ከተሳታፊዎች መካከል ዶ/ር ዳዊት ጀቦ፣ አቶ አብርሃም መኩሪያ እና ሌሎች ከህብረተሰቡ በመግባባት ሲሠሩ መቆየታቸውን በመግለጽ የመመዝገቢያ ኪት ችግር እንደነበረም አስታውቀዋል።‎

‎ለ2019 በጀት ዓመት አፈጻጸም ህብረተሰቡ በስፋት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የግንዛቤ ሥራ በመሥራት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ የበኩላቸውን እንደሚወጡም ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።‎

‎ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን