ዞኑ ይህን በዩኔስኮ የተመዘገበ ዓለም አቀፍ ቅርስ በዘላቂነት ለመጠበቅ እንዲቻል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡
የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ቅርስ ሰውና ተፈጥሮ ተዋህዶ መኖር እንደሚችል የሚያሳይ በመሆኑ በዩኔስኮ መመዝገቡ አንዱ ማሳያ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ተፈጥሮ የቸረችውን ውብና ፀጋ ቅርስ ከአደጋ በመታደግ እና በዘላቂነት በመጠበቅ የቱሪስት መዳረሻና የኢኮኖሚ ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስተዳዳሪው አብራርተዋል ።
የዓለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው መልክዓ ምድሩ ባህላዊ እሴቱን ሳይለቅ ለቀጣዩ ትውልድ የማሻገር ስራ እየተሠራ እንደሚሀኝ የገለፁት አስተዳዳሪው ለውጤታማነቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
የዞኑ ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊው አቶ እድሉ ታደሰ አባቶች በትውልድ ቅብብሎሽ ጠብቀው ያቆዩትን ቅርስ በመንከባከብና በመጠበቅ ወደ ትውልድ ለማሻገር ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በመድረኩ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሕይወት ኃይሉ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይንቱ መልኩ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ጨምሮ የክልል ምክትል የቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ታድመዋል ።
ዘጋቢ: ፅጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ