በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ
በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ገበያ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ፤ በለውጡ ዓመታት የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች መከናወናቸውን በመጠቆም ፓርቲው ዜጎችን በሁሉም ዘርፎች የሚያሳትፍ አካታችና አሳታፊ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
አክለውም ምርጫ ለአንድ አገር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት መሆኑን በመጠቆም ህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቀሞ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከርና ልማትን ለማፋጠን ያስችላል የሚለውን ፓርቲ መምረጥ እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ማድረግ የሚያስችል አስተማማኝ መሠረት መጣሉን አስገንዝበዋል።
የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ፤ ፓርቲው በጌና ወረዳና በአካባቢው እያከናወናቸው ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች የህዝቡን ህይወት በመቀየር ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
እነዚህን የልማት ሥራዎች አጠናክሮ ለማስቀጠልና የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ኅብረተሰቡ ከፓርቲው ጎን በመቆም የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፉ ላይ የተገኙት የወረዳው ነዋሪዎች እንደገለፁት፤ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሀገሪቱ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
በተለይም ለሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በተሰጠው ትኩረት በሌማት ትሩፋት፣ ለአቅመ ደካሞች ቤቶች ግንባታና በሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እየሆነ ነው ብለዋል።
በምረጡኝ ቅስቀሳው ብልጽግና ፓርቲን በየደረጃው የሚወክሉ እጩዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፈ ግዛው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የቡና ኮንፈረንስ ተጠናቋል
ባህላዊ እሴትና የወንድማማችነት ትስስርን የሚያድስ የ“ኦዴ ኦሶ” ቤተሰብ ምረቃ ስነ-ስርዓት በልዩ ድምቀት ተካሄደ