በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።
የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖራቸው ቆይታ የእንስሳት መሸጫ ገበያ ማዕከላትን፣ የመኖና መስኖ ልማት ሥራዎችን፣ የተማሪዎች ሆስቴል አገልግሎትን፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሌሎች የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሠሩ መሠረተ ልማቶችን ምልከታ ያደርጋሉ ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ