በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።
የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖራቸው ቆይታ የእንስሳት መሸጫ ገበያ ማዕከላትን፣ የመኖና መስኖ ልማት ሥራዎችን፣ የተማሪዎች ሆስቴል አገልግሎትን፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሌሎች የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሠሩ መሠረተ ልማቶችን ምልከታ ያደርጋሉ ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የብራይት ፕሮጀክት የሴቶችንና ህፃናትን የስራ ጫና ከማቃለል ባሻገር የንፁህ መጠጥ ውሀ ተደራሽነት ላይ የሚመታይ ተግባር ማከናወኑን የጋሞ ዞን ውሀና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጥናታቸው በተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ ወርክሾፕ እና የርክክብ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል
የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የቤት ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ