በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።
የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖራቸው ቆይታ የእንስሳት መሸጫ ገበያ ማዕከላትን፣ የመኖና መስኖ ልማት ሥራዎችን፣ የተማሪዎች ሆስቴል አገልግሎትን፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሌሎች የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሠሩ መሠረተ ልማቶችን ምልከታ ያደርጋሉ ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት መንግስት የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የአርባምንጭ ከተማ ሸማቾችና ነጋዴዎች ጠየቁ
ባንኩ አዳዲስ የዲጂታል አገልግሎቶች መጀመሩን አስታወቀ
ባለፉት 8 የለውጥ ዓመታት የህዝቡንና የሀገሪቱን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሳው (ዶ/ር) ገለፁ