በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የተመራው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።
የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት በሁለት ተከታታይ ቀናት በሚኖራቸው ቆይታ የእንስሳት መሸጫ ገበያ ማዕከላትን፣ የመኖና መስኖ ልማት ሥራዎችን፣ የተማሪዎች ሆስቴል አገልግሎትን፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሌሎች የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሠሩ መሠረተ ልማቶችን ምልከታ ያደርጋሉ ተብሎም ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክረምቱ ወቅት የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም ከማስቻሉም በላይ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጅት ከፍተኛ እገዛ እያደረገላቸው መሆኑን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ገለፁ
የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ እና የግብርና ቴክኖሎጂን በተገቢ መጠቀም ከጀመሩ ወዲህ ምርትና ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን በከምባታ ዞን የዶዮገና ወረዳ አንዳንድ አርሶ አደሮች ተናገሩ
የኦዲት አገልግሎት ቅልጥፍናና ጥራት በማሣደግ የተገልጋይና የባለድርሻ አካላት ርካታን ለማሣደግ እየተከናወነ በሚገኘው ተግባር ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ዋና ኦዲተር አስታወቀ