ሀዋሳ፡ ጥር 15/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዘንድሮ በልግ 182 ሺህ 843 ሔክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡
የበልግ እርሻ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረው ዞናዊ መድረክ በአርባ ምንጭ እየተካሔደ ነው።
በዞኑ ያሉ ምቹ የግብርና ጸጋዎችን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ አየተሠራ መሆኑን የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ወርቅነህ ካልሳ ተናግረዋል።
በዘንድሮ የበልግ እርሻ ለማልማት ዞናዊ ንቅናቄ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ወርቅነህ አንድም መሬት ጾም እንዳያድር ሁሉንም አቅሞችን እንጠቀማለን ነው ያሉት።
የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ማጌሶ ማሾሌ፤ በዘንድሮው የበልግ እርሻ ከ34 ሚሊየን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
በምርት ዘመኑ 182 ሺህ 843 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ግብ ተጥሎ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፥ ከ34 ሚሊየን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱንም ሀላፊው አስረድተዋል።
በበልግ እርሻ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የግብዓት አቅርቦት፣ ቅንጅታዊ አሰራሮችና ድጋፋዊ ክትትሎች ሊጠናከሩ ይገባል ያሉት የዞኑ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ገዛኸኝ ጋሞ ናቸው።
የተለያዩ ሰብሎችን በማምረት የዞኑን ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት መሠራት እንዳለበት የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች በአስተያየታቸው አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገር ተግባርን እውን ለማድረግ የተቀናጀ የግብርና ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ ገለፀ
የህዝቡን ዘላቂ ሠላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ የፀጥታ አካላት የጋራ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ቦታዎች ለምተው የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ እንክብካቤ ማድረግና ከንክኪ ነፃ መሆን እንዳለባቸው የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ አሳሰቡ