በከተማ ያለውን ህገወጥ የንግድ ስርዓት እና ኮንትሮባንድን በማስቀረት ህጋዊ ነጋዴዎችን የመደገፍ እና የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ህገወጥ የንግድ ስርዓት እና ኮንትሮባንድን በማስቀረት ህጋዊ ነጋዴዎችን የመደገፍ እና የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ የከተማው ከንቲባ ኢንጅነር ሰለሞን ለዊ ተናገሩ።
“ሁለንተናዊ ብልጽግና የማህበረሰቡ ሚና” በሚል ከሚዛን አማን ከተማ ንግድ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት የተገኙት የሚዛን አማን ከተማ ከንቲባ ኢንጅነር ሰለሞን ለዊ እንደተናገሩት በከተማው እየተመዘገበ ላለው ፈጣን እድገት፥ የንግዱ ማህበረሰብ ድርሻ ትልቅ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በከተማው በተለይም የታማኝ ግብር ከፋዮች ውጤት ትልቅ መሆኑን ጠቁመው፥ ለዚህም በተከናወኑ የከተማ መልሶ ግንባታ እና የኮሪደር ልማት ተግባራት አማላካች እንደሆነ ተናግረው፥ የሞዴል ትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ የሰላም እና ጸጥታ ተግባራቶች በተለይም ከለውጡ በኋላ በብልጽግና የተገኙ ውጤቶች መሆናቸውን ኢንጅነር ሰለሞን አስረድተዋል።
የንግዱን አከባቢ ምቹ ከማድረግ ባለፈ ህገወጥ እና የኮንትሮባንድ ንግድ ቁጥጥር ተግባራትን በማጠናከር የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመዋው፥ የንግዱ ማህበረሰብ ከከተማ አስተዳደሩ ጎን መቆም ይጠበቅበታል ብለዋል።
ከፊታችን የሚካሄደው ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ የንግዱ ማህበረሰብ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እንዲጠቀሙ ኢንጅነር ሰለሞን ለዊ ጥሪ አቅርበዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር እየተካሄደ ባለው ውይይት የከተማ ኢንዱስትሪ እና ንግድ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው መለሰ የውይይት ሰነድ የቀረበ ሲሆን፥ በከተማው ከስድስት ሺ በላይ በተለያዩ የንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ነጋዴዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 875 ሚሊዬን ብር ገቢ መሰብሰቡንም ጠቁመው፥ ይህም በከተማው ለተከናወኑት የልማት ተግባራት ማዋል መቻሉን ገልጸው፥ የተጀመረውን የልማት ስራ ለማስቀጠል የንግዱ ማህበረሰብ ከከተማ አስተዳደሩ ጎን መቆም ይጠበቅበታልም ብለዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት እያደረገ ይገኛል።
ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ