ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ

ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፍተዋል፡፡

ትምህርት ቤቱ በሀገር ደረጃ ለሞዴል ትምህርት ቤቶች ግንባታ በተያዘው ኢኒሼቲቪ መነሻ የተተገበረ መሆኑም በዚሁ ወቅት ተመላክቷል።

የባሌ ከተማ አስተዳደር ከተዋቀረ በኋላ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢኒሼቲቪ የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።

ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ በአካባቢው ማህበረሰብና በጎ አድራጎት ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ መገንባቱም ተመላክቷል።

ትምህርት ቤቱ በአካባቢው መገንባቱ ለህጻናት ክህሎት ማበልጸጊያ ያለው ድርሻ የላቀ መሆኑ ተጠቁሟል።

በቀጣይ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲፈጠር አበርክቶው የላቀ ነውም ተብሏል።

ዘጋቢ፡ አዲስዓለም ታዬ – ከዋካ ጣቢያችን