ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፍተዋል፡፡
ትምህርት ቤቱ በሀገር ደረጃ ለሞዴል ትምህርት ቤቶች ግንባታ በተያዘው ኢኒሼቲቪ መነሻ የተተገበረ መሆኑም በዚሁ ወቅት ተመላክቷል።
የባሌ ከተማ አስተዳደር ከተዋቀረ በኋላ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢኒሼቲቪ የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ በአካባቢው ማህበረሰብና በጎ አድራጎት ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ መገንባቱም ተመላክቷል።
ትምህርት ቤቱ በአካባቢው መገንባቱ ለህጻናት ክህሎት ማበልጸጊያ ያለው ድርሻ የላቀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በቀጣይ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዲፈጠር አበርክቶው የላቀ ነውም ተብሏል።
ዘጋቢ፡ አዲስዓለም ታዬ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ