ሪያል ማድሪድ ኢብራሂማ ኮናቴን ማስፈረም አይፈልግም
የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ የሊቨርፑሉን የመሀል ተከላካይ ኢብራሂማ ኮናቴን ማስፈረም እንደማይፈልግ ተገልጿል።
በያዝነው የውድድር ዓመት መጨረሻ በሊቨርፑል ቤት ያለው ኮንትራት የሚጠናቀቅበት ኢብራሂማ ኮናቴ በሪያል ማድሪድ በጥብቅ እንደሚፈለግ ሲነገር ቆይቷል።
እንደ ፋብሪዚዮ መረጃ መሰረት ሪያል ማድሪድ አሁን ላይ ግን ፈረንሳዊውን ተጫዋች የማስፈረም ፍላጎት እንደሌለው እና ከዝውውሩ ራሱን ማውጣቱን ለሊቨርፑል አሳውቋል።
የ26 ዓመቱ ተከላካይ ኢብራሂማ ኮናቴ እንደ አውሮፓውያኑ በ2021 በ36 ፓውንድ ከጀርመኑ ክለብ አርቢ ላይፕዚች ለመርሲሳይዱ ክለብ መፈረሙ ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አሽሊ ያንግ ጫማውን ሰቀለ
“በቀጣይ የውድድር ዘመን የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ማንሳት እንችላለን” — ሜሰን ማውንት
ከሚያዝያ 22 ጀምሮ በጂንካ ከተማ ለሚስተናገደው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ግምገማ መካሄዱን የክልሉ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከስታወቀ