ማርቲን ኦዴጋርድ ወደ ልምምድ ተመለሰ
የአርሰናሉ አምበል ማርቲን ኦዴጋርድ ከጉዳቱ በማገገም ወደ ልምምድ መመለሱ ተገልጿል።
ኖርዊያዊው የመሀል ስፍራ ተጫዋች በትከሻ ጉዳት ምክንያት ለሁለት ወራት ከሜዳ መራቁ ይታወሳል።
በነዚህ ግዚያት ውስጥም ሁለት የብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታዎች እና 12 የአርሰናል ጨዋታዎች አልፈውታል።
አሁን ላይ ግን ኦዴጋርድ መድፈኞቹ በነገው ዕለት ከባየርንሙኒክ ጋር ከሚያደርጉት ወሳኝ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ በፊት በአርሰናል የልምምድ ማዕከል ተገኝቶ ከቡድን አጋሮቹ ጋር በጋራ ልምምድ መስራቱ ተነግሯል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አሽሊ ያንግ ጫማውን ሰቀለ
“በቀጣይ የውድድር ዘመን የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ማንሳት እንችላለን” — ሜሰን ማውንት
ከሚያዝያ 22 ጀምሮ በጂንካ ከተማ ለሚስተናገደው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ግምገማ መካሄዱን የክልሉ እግር ኳስ ፌደሬሽን ከስታወቀ