ማርቲን ኦዴጋርድ ወደ ልምምድ ተመለሰ
የአርሰናሉ አምበል ማርቲን ኦዴጋርድ ከጉዳቱ በማገገም ወደ ልምምድ መመለሱ ተገልጿል።
ኖርዊያዊው የመሀል ስፍራ ተጫዋች በትከሻ ጉዳት ምክንያት ለሁለት ወራት ከሜዳ መራቁ ይታወሳል።
በነዚህ ግዚያት ውስጥም ሁለት የብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታዎች እና 12 የአርሰናል ጨዋታዎች አልፈውታል።
አሁን ላይ ግን ኦዴጋርድ መድፈኞቹ በነገው ዕለት ከባየርንሙኒክ ጋር ከሚያደርጉት ወሳኝ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ በፊት በአርሰናል የልምምድ ማዕከል ተገኝቶ ከቡድን አጋሮቹ ጋር በጋራ ልምምድ መስራቱ ተነግሯል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ