ሀገሪቱን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር በማህበራዊም ሆነ በኢኮኖሚ ዘርፍ ተጠቃሚ ለማደረግ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ
ጽ/ቤቱ “ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ቃል የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ዙሪያ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።
መድረኩ ባለፉት ጊዜያት የነበሩ ስኬቶችንና ችግሮችን በመለየት ለቀጣይ ውይይት በማድረግ ለጋራ ችግሮች በጋራ መፍትሔ መፈለግ ላይ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ጅክሶ፣ በሀገራችን ስር ሰዶ የቆየውን የተረጂነትና የልመና አስተሳሰብ ለማስወገድ ህዝቡን ወደ ላቀ ምርታማነት ደረጃ ማሸጋገርና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተሠራ መቆየቱን ተናግረዋል።
በቀጣይም ሀገሪቱን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር በማህበራዊም ሆነ በኢኮኖሚ ዘርፍ ተጠቃሚ ለማደረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ ኃላፊው አስገንዝበዋል።
በመድረኩ ላይ የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔን ጨምሮ የወረዳው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የተለያዩ አደረጃጀቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘርሁን ሹፌር – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ