ከባለፉት 5 ዓመታት በተለየ የውድድር ቅርፅ በሁለት ምድቦች ተከፍሎ የሚካሄደው የዚህ ውድድር ዓመት የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በዛሬው ዕለት ሀዋሳ እና አዲስ አበባ ላይ ጅማሮውን ያደርጋል።
በፕሪሚየር ሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ በሁለት ስታዲየሞች በድምሩ አራት ፍልሚያዎች የሚከናወኑ ይሆናል።
በዚህም መሰረት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ከሲዳማ ቡና ጋር ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ድሬዳዋ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ የሚጫወቱ ይሆናል።
ከስድስት ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ለማስተናገድ በተዘጋጀው የአዲስ አበባ ስታዲየም ላይ የዘንድሮው የውድድር ዓመት የመክፈቻ መርሐግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከሸገር ከተማ ጋር ይገናኛል።
ጨዋታው ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ይካሄዳል።
10 ሰዓት ላይ ደግሞ አርሲ ነገሌ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ይጫወታሉ።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ