ሊድያ ታፈሰ የካፍ የዳኞች ኮሚቴ አባል ሆና ተመረጠች
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቀድሞ ዓለም አቀፍ ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ የካፍ የዳኞች ኮሚቴ አባል ሆና ተመርጣለች።
የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ በመሆን እያገለገለች የምትገኘው ሊዲያ ታፈሰ ካፍ በአዲስ መልክ ባዋቀረውና 12 አባላት ባሉት ኮሚቴ አባል ሆና መመረጧን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
ሊዲያ ታፈሰ የዳኞች ኢንስትራክተር መሆኗ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ማርክ ጉሂን ለማስፈረም ተስማማ
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ