አርሶአደሩ አረምና ተባይን በመቆጣጠር ምርትና ምርታማነትን እንዲያሳድግ እየተሠራ መሆኑን የኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
በ2018 መኸር እርሻ ከ1 ሚሊዮን 50 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታውቋል።
በኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ አሸናፊ አሳምነው፤ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ70 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን ገልጸው በአብዛኛው ከአንድ ጊዜ በላይ የአረም ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በዞን ደረጃ የመኸር እርሻ ከዕቅድ በላይ መሸፈኑን የገለጹት ቡድን መሪው 1 ሚሊዮን 54 ሺህ ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በዞኑ ጎርካ ወረዳ በዝናብ እጥረት የአረም ቁጥጥር መጓተቱን ያነሱት አቶ አሸናፊ፤ በአሁኑ ወቅት ባለው እርጥበት አርሶአደሩ አረምና ተባይን በመቆጣጠር ምርትና ምርታማነትን እንዲያሳድግ አሳስበዋል።
ከዞቀሳና ጋሙሌ ቀበሌ ያነጋገርናቸው አርሶአደር ገላዬ ጩሉሲ እና ዘለሉ አየለ ለረዥም ሳምንታት ተቋርጦ የነበረው ዝናብ በመጀመሩ በእጅ በማረምም ሆነ ፀረ አረም በመርጨት አረምን የመቆጣጠር ተግባር ላይ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
አርሶአደሩ አረምና ተባይን በመቆጣጠር ምርትና ምርታማነትን እንዲያሳድግ እየተሠራ መሆኑን የኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ