ምግብና ሥርዓተ-ምግብን በማሻሻል የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ገለጸ
በቢሮው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ከምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለእንስሳት እርባታ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየተሰጠ ነው።
በስልጠናው መድረክ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታመነ በቀለ፤ ባለፉት አራት አመታት በሌማት ትሩፋት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የተሻለ መነቃቃት የታየባቸው ናቸው ብለዋል።
ቢሮው ምግብና ሥርዓተ-ምግብን በማሻሻል የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነም ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት ሥራን ከተለመደው የእርባታ ዜደ የተሻለ በማድረግ በምርቶች ላይ እሴት በመጨመር የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የእንስሳት ተዋጽኦ በኢትዮጵያዊያን ማዕድ ላይ የቅንጦት ምግብ መሆን የለበትም ያሉት አቶ ታመነ፤ ያሉንን ሀብቶች ተጠቃሚ ለመሆን ጠንክሮ መስራት ይጠይቃል ብለዋል።
በክልሉ በእንስሳት እርባታው ዘርፍ ከ15 እስከ 20 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ጠቁመው፤ በቀጣይ በስፋት መስራትና የማሳደግ ተግባር የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ ይሆናል ብለዋል።
በሌማት ትሩፋት ፓኬጅ ላይ የተዘጋጀውን የስልጠና ሰነድ በቢሮው የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ መሰለች ታደመ እያቀረቡ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክረምቱ ወቅት የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም ከማስቻሉም በላይ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጅት ከፍተኛ እገዛ እያደረገላቸው መሆኑን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ገለፁ
የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ እና የግብርና ቴክኖሎጂን በተገቢ መጠቀም ከጀመሩ ወዲህ ምርትና ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን በከምባታ ዞን የዶዮገና ወረዳ አንዳንድ አርሶ አደሮች ተናገሩ
የኦዲት አገልግሎት ቅልጥፍናና ጥራት በማሣደግ የተገልጋይና የባለድርሻ አካላት ርካታን ለማሣደግ እየተከናወነ በሚገኘው ተግባር ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ዋና ኦዲተር አስታወቀ