በሩብ አመቱ 1ሺህ 600 ሄ/ር መሬት ለአልሚ ባለሀብቶች መተላለፍ መቻሉ ተገለጸ

በሩብ አመቱ 1ሺህ 600 ሄ/ር መሬት ለአልሚ ባለሀብቶች መተላለፍ መቻሉ ተገለጸ

ሀዋሳ፡ መስከረም 27/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በተጠናቀቀው ሩብ ዓመት 1ሺህ 600 ሄ/ር መሬት ለአልሚ ባለሀብቶች ማስተላለፍ መቻሉን የቤንች ሸኮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ገለፅ።

‎የቤንች ሸኮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኮጅ ባዳካች እንደገለፁት ዞኑ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት ያለበት እንደሆነ ጠቁመው፥ በበጀት ዓመቱ በአገልግሎት፣ በግብርናና በኢንዱስትሪ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል ።

‎በተጠናቀቀው ሩብ ዓመት 2ሺ ሄ/ር መሬት ለመለየት ታቅዶ 3ሺ 761 ሄ/ር የመለየት ስራ መሰራቱን አቶ ኮጅ ተናግረዋል ።

‎በዚህም በ2017 ተለይቶ ባለቤት ለተፈጠረላቸው አልሚዎች መሬት ማስረከብ ብቻ ሳይሆን ወደ ስራ ገብተው ማልማት እንዲችሉ በርካታ ስራዎች መሰራቱን አመላክተዋል።

‎የተለዩ መሬቶችን እንዲያለሙ በግብርና 8፣ በኢንድስትሪ 5፣ በአገልግሎት 6 በአጠቃላይ 19 ፕሮጆክቶች ላይ ፍቃድ የመስጠት ስራ ከማከናወን ባለፈ 5 ነባር ኢንቨስትመንቶች ፍቃድ እንዲያድሱ ታቅዶ ሁለት ኢንቨስትመንት እድሳት ማድረጋቸውን አቶ ኮጅ ባዳካች ተናግረዋል።

‎በዘርፉ የተሳተፉ ከ108 ሚሊዬን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ሲሆኑ እነዚህም በ8 ኢንበስትመንት በዚህ ሩብ ዓመት 1ሺ 600ሄ/ር መሬት ማስረከብ መቻሉን የመምሪያው ሃላፊ ተናግረዋል ።

‎ኢንቨስትመንት ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋፆ ከፍተኛ ነው ያሉት አቶ ኮጅ በዞኑ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለ ገልፀው ይህንን ሁሉም መዋቅር የመሬት አቅማቸውን ለይተው ጥናት በማድረግ ዘርፉን ማበልፀግ ይገባል ብለዋል ።

‎ዞኑ ሰፊ የሆነ ለሆቴል ቱሪዝም፣ የግብርናና የማዕድን፣ ፀጋዎችን የታደለ በመሆኑ ባለሀብቶች ወደ አካባቢው መጥተው እንዲያለሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ዘጋቢ፡ ‎ዮናስ ወ/ገብሬኤል – ከሚዛን ጣቢያችን