በክረምት ወራት የታየውን ትጋት በበጋውም ለመድገም ቁርጠኞች መሆናቸውን በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ
በከተማው የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ እና የ2018 ዓ.ም የበጋውን ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሂዷል።
በከተማው በአምናው የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናወኑ ተግባራት የበርካታ ወገኖችን እንባ ያበሰ እንደነበረ ነው የተገለጸው።
በወጣቶቹ አገልግሎት 3 መቶ 42 የሚሆኑ የአቅመ ደካሞች ቤቶች ግንባታና እድሳት አንደተከናወነ የተገለፀ ሲሆን በከተማ ጽዳት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናዉነዋል ተብሏል።
ከ18 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በተሰማሩበት በዚህ በጎ ተግባር ከ79 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወገኖች ተጠቃሚ መሆናቸውንና አገልግሎቱ በገንዘብ ሲተመን ከ29 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚሆንም ተገልጿል።
በእነዚህ በጎ ተግባራት ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል ወጣት አማከለች አየለ፣ ይታገሱ ወርቁ እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት በክረምት ወራት በነበረው አገልግሎት በተለያዩ ተጽዕኖዎች ሳይገደቡ በትጋት ሲሠሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው በበጋዉም ለመድገም ቁርጠኞች መሆናቸውን አስረድተዋል።
በከተማው አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባህሩ ማሞ በበኩላቸው ባለፈው ዓመት የተመዘገበው የቅንጅት ውጤት እንደሆነ ገልጸው በበጋውም ለመድገም እየሠሩ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግሥቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የተለያዩ የህክምና መድሀኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት መቻላቸውን በሚዛን አማን ከተማ በማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ ሲገለገሉ ያገኘናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ገለፁ
የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በደማቅ ስነ ስርዓት በሣጃ ከተማ እየተከበረ ነው
ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን አስመልክቶ በተዘጋጀው መሪ ዕቅድ ዙሪያ የዉይይት መድረክ ተካሄደ