ፕሮጀክቱን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ ዞን የዎባ አሪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) 30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ ዞን የዎባ አሪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገልፀዋል፡፡
የወረዳውን የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለፍራፍሬና ቅባት እህሎች በመጠቀም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የወረዳው አስተዳደር እንደሚሠራ አስታውቋል፡፡
በደቡብ ኦሞ ዞን ዎባ አሪ ወረዳ የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት ሁለተኛ ዓመት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የወረዳው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙት ተከናውኗል፡፡
በችግኝ ተከላው የተገኙ አርሶ አደሮች እንደተናገሩት፤ ፍራፍሬዎች ለኑሮአችን ዋስትና ስለሆኑ የተተከለው ችግኝ ፀድቆ ፍሬ እስኪያፈራ እንክብካቤ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡
በወረዳው ለግብርና ዕድገት ማነቆ የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየሠሩ መሆናቸውን የገለፁት የግብርና እድገት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ቢሻው መካሪ ናቸው፡፡
የዎባ አሪ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽብሩ ተካልኝ እንደተናገሩት፤ ለማህበረሰቡ በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኝ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ማቅረባቸውን ገልፀው አምና የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች 89 በመቶ መፅደቃቸውን አስረድተዋል፡፡
የወረዳውን የተፈጥሮ ፀጋዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢያሱ ዘርፉ ህዝቡ ለፍራፍሬ ልማት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
ምግብና ሥርዓተ-ምግብን በማሻሻል የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ገለጸ
የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በምርምር የተረጋገጡ አዳዲስና የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ
የቀይ አፈር ሙሉ ወንጌል ነህምያ የልጆች ልማት ከደቡብ ኦሞ ዞን ሴቶችና ሕፃናት መምሪያ ጋር በመተባበር “የዎና ናና” የህፃናት ልማት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በዲመካ ከተማ ተካሂዷል