ፕሮጀክቱን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ ዞን የዎባ አሪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) 30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ ዞን የዎባ አሪ ወረዳ አርሶ አደሮች ገልፀዋል፡፡
የወረዳውን የተፈጥሮ ፀጋዎችን ለፍራፍሬና ቅባት እህሎች በመጠቀም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የወረዳው አስተዳደር እንደሚሠራ አስታውቋል፡፡
በደቡብ ኦሞ ዞን ዎባ አሪ ወረዳ የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት ሁለተኛ ዓመት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የወረዳው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙት ተከናውኗል፡፡
በችግኝ ተከላው የተገኙ አርሶ አደሮች እንደተናገሩት፤ ፍራፍሬዎች ለኑሮአችን ዋስትና ስለሆኑ የተተከለው ችግኝ ፀድቆ ፍሬ እስኪያፈራ እንክብካቤ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡
በወረዳው ለግብርና ዕድገት ማነቆ የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየሠሩ መሆናቸውን የገለፁት የግብርና እድገት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ቢሻው መካሪ ናቸው፡፡
የዎባ አሪ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽብሩ ተካልኝ እንደተናገሩት፤ ለማህበረሰቡ በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኝ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ማቅረባቸውን ገልፀው አምና የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች 89 በመቶ መፅደቃቸውን አስረድተዋል፡፡
የወረዳውን የተፈጥሮ ፀጋዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢያሱ ዘርፉ ህዝቡ ለፍራፍሬ ልማት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ