በአዲስ አበባ ለሦስት ቀናት የተካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ዕድል መፍጠሩ ተመለከተ፡፡
የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አቅም ለማስተዋወቅ ላለፉት ሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው “ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2023 ፎረም” ዛሬ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ፎረሙ ኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ማስተዋወቅ የቻለችበት ነው ብለዋል፡፡
በዚህም አዳዲስ የውጭ ኩባንያዎች ወደ ኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲገቡ ፎረሙ ዕድል መፍጠሩን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
አምስት ግዙፍ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችን ጨምሮ ከሌሎች ኩባንያዎች ጋር የኢንቨስትመንት ሥምምነት በማድረግ ፎረሙ በስኬት መጠናቀቁን ነው ያመላከቱት፡፡
ይህም በ2015 በጀት ዓመት ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለማምጣት ለተያዘው ዕቅድ ትልቅ ድርሻ አለው ነው ያሉት፡፡
ለኢንቨስትመንት ጥበቃ ማድረግና የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍታት መንግሥት ለዘርፉ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል መሆኑንም ነው ያስገነዘቡት፡፡
የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) መንግሥት ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ፖሊሲዎችና የተለያዩ የሪፎርም ሥራዎችን ተግባራዊ እያደረገ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ግብርና፣ ማዕድን፣ አይሲቲ፣ ቱሪዝምና ማኑፋክቸሪንግ ቁልፍ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንደሚሆኑ ገልጸው ባለሃብቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።