በቡርጂ ዞን ለሚገኙ የተለያዩ አቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ

በቡርጂ ዞን ለሚገኙ የተለያዩ አቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ

ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቡርጂ ልማት ማህበር ከዞኑ የተለያዩ አከባቢዎች ለተወጣጡ አቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።‎

‎በመረሃ ግብሩ የተገኙት የቡርጂ ዞን ብልፅግና ፓርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡሜ ቾኮል የትምህርት ዘርፍ የህልውና ጉዳይ ስለሆነ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጠቁመው፥ ልማት ማህበሩ ህብረተሰቡን በማስተባበር ለሰራው የድጋፍ ማሰባሰብ ሥራ አመስግነዋል፡፡‎

‎የቡርጂ ልማት ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ በርሱ ህርባዬ በበኩላቸው፥ የትምህርት ብክነት ለማስቀረት እና መጠነ ማቋረጥ ለመቀነስ ድጋፉ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው፥ ትልቁ ግባችን የተደገፉ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጨርሰው ማየት ነው ብለዋል።‎

‎የቡርጂ ልማት ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ማርቆስ ጩሙኦ፥ በ5 ቀናት ወስጥ ከ47 ሺህ ብር በላይ ከህብረተሰቡ በማሰባሰብ 50 ለሚሆኑ ተማሪዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን አንስተው ለጥያቄያቸው በጎ ምላሽ የሰጡ የህብረተሰብ ክፍሎችንም አመስግነዋል ።‎

ድጋፉ ከተደረገላቸው ተማሪዎች መካከል ተማሪ ብሌን ወየሳ እና ተማሪ ምርቃት አይላሞ በሰጡት አስተያየት የተደረገላቸው ድጋፍ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ የሚያደርግ በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን አንስተው ድጋፉ ቀጣይነት እንዲኖረውም ጠይቀዋል፡፡

ዘጋቢ ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን