የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራት ነው – የኮሬ ዞን አስተዳደር
ሀዋሳ፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የጥቁር ህዝቦች ኩራት መሆኑን የኮሬ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡
በኮሬ ዞን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን በተመለከተ በፓናል ውይይትና በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል ።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ታላቁ የህዳሴ ግድባችንን የኢትዮጵያውያን ተጋድሎ የታየበትና ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካዊያን ኩራት መሆኑን ገልጸዋል ።
የእንጉርጉሮ ዘመን አብቅቶ የህዳሴ ግድብ ተመርቆ በአይናችን አይተናል ያሉት አስተዳዳሪው፥ በዚህ ብቻ ሳንገታ ኢትዮጵያን ለአለም ሊያሳዩ የሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን መስራት እንደሚቻል ይህ ማሳያ እንደሆነ ነው የተናገሩት ።
የኮሬ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ሳድሁን በበኩላቸው የህዳሴ ግድብ፣ ኢትዮጵያ ታላቅነቷ በአለም መድረክ የታየበት፣ የአንድነታችን ማረጋገጫ ካርታችን ነው ብለዋል ።
በኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት በብልጽግና ተምሳሌት የህዳሴ ግድባችንን አጠናቀናል፤ በሌሎች ሀገራዊ ስራዎች በህዳሴ ያሳየነውን አንድነትና ቁርጠኝነት ማስቀጠል ይገባናል ነው ያሉት ።
የውይይቱ ተሳታፊዎችም የህዳሴ ግድባችን የነበሩ ልዩነቶችን ያጠበበ፣ በራሳችን ገንዘብና ላብ የተገነባ የሁላችንም አሻራ ያረፈበት ነው ሲሉ ገልጸዋል ።
እኛም የዚህ ትውልድ አካል በመሆናችን ዕድለኞች ነን የሚሉት ተሳታፊዎቹ በሌሎችም ፕሮጀክቶች አንድነታችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅን አስመልክቶ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ መሪ ቃሎችና የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍየዕለቱ ዝግጅት ተጠናቋል።
ዘጋቢ: ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመረጃ ጥራት ዙሪያ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተጠቆመ
የሀገሪቱን የሥጋ ምርት ጥራትና መጠን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉ አቀፍ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ