የዋቸሞ ዩንቨርስቲ አዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 50 ቤተሰቦች ለበዓል መዋያ የሚሆን እህልና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ድጋፍ የተደረገላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች በበኩላቸው የተሰጣቸው ድጋፍ በዓሉን ያለ ሀሳብ እንዲያሳልፉ ስለረዳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ ዩንቨርስቲው ከመማር ማስተማር ስራ ጎን ለጎን በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዕለቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 50 ቤተሰቦች አዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ የበዓል መዋያ እንዲሆናቸው 50 ኪሎ ጤፍ፣ 3 ሊትር ዘይት፣የዶሮ እንቁላልና የልብስ ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን ከ380 ሺህ ብር በላይ እንደሆነም አመላክተዋል።
ተቋሙ የአረጋውያንና ሕጻናት ማዕከል ከመደገፍ ባለፈ በቀጣይም ተመሳሳይ ተግባር ለመፈጸም ቁርጠኛ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ሁሉም ሰው ካለው በማካፈል አብረው የማብላት ልማድ ማድረግ እንደለበትም ዶክተር ዳዊት መክረዋል።
ድጋፍ ከተደረገላቸው ማሕበረሰብ መካከል ወ/ሮ አማራች ቤያኮ እንደገለጹት ተፈናቃይ ከመሆናቸው የተነሳ ልጆቻቸውን ይዞ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ ባሉበት ወቅት የእህልና ምግብ ነክ ቁሳቁስ ድጋፍ መገኘታቸው እንዳስደሰታቸው ጠቁመዋል።
ሌሎች ድጋፍ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በበኩላቸው ድጋፉ በዓሉን ያለ ሀሳብ እንዲያሳልፉ ስለረዳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- ጌታቸው መጮሮ ከሆሳዕና ጣቢያ

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ