የዋቸሞ ዩንቨርስቲ አዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 50 ቤተሰቦች ለበዓል መዋያ የሚሆን እህልና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ድጋፍ የተደረገላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች በበኩላቸው የተሰጣቸው ድጋፍ በዓሉን ያለ ሀሳብ እንዲያሳልፉ ስለረዳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ ዩንቨርስቲው ከመማር ማስተማር ስራ ጎን ለጎን በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዕለቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 50 ቤተሰቦች አዲሱን ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ የበዓል መዋያ እንዲሆናቸው 50 ኪሎ ጤፍ፣ 3 ሊትር ዘይት፣የዶሮ እንቁላልና የልብስ ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን ከ380 ሺህ ብር በላይ እንደሆነም አመላክተዋል።
ተቋሙ የአረጋውያንና ሕጻናት ማዕከል ከመደገፍ ባለፈ በቀጣይም ተመሳሳይ ተግባር ለመፈጸም ቁርጠኛ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ሁሉም ሰው ካለው በማካፈል አብረው የማብላት ልማድ ማድረግ እንደለበትም ዶክተር ዳዊት መክረዋል።
ድጋፍ ከተደረገላቸው ማሕበረሰብ መካከል ወ/ሮ አማራች ቤያኮ እንደገለጹት ተፈናቃይ ከመሆናቸው የተነሳ ልጆቻቸውን ይዞ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ ባሉበት ወቅት የእህልና ምግብ ነክ ቁሳቁስ ድጋፍ መገኘታቸው እንዳስደሰታቸው ጠቁመዋል።
ሌሎች ድጋፍ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በበኩላቸው ድጋፉ በዓሉን ያለ ሀሳብ እንዲያሳልፉ ስለረዳቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- ጌታቸው መጮሮ ከሆሳዕና ጣቢያ

More Stories
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ
በሀገሪቱ ያለው 80 በመቶ ቡና ያረጀ በመሆኑ መታደስ እንደሚገባ ተጠቆመ