በከተማው የሚገኙ እግር ኳስ ቡድኖች ተወዳዳሪና ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚያደርጉት በጎ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የአርባምጭ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የአርባምንጭ ከተማ እርሻ ጤና እግር ኳስ ቡድን በአካባቢው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖች የትምህርትና ለዘመን መለወጫ የሚሆን የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኃይለገብርኤል ሴኮ በከተማው ከሚገኙ የእግር ኳስ ቡድኖች ተወዳዳሪና ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ የተለያዩ በጎ ተግባራትን እያከናወኑ መሆናቸውን ገልፀው፤ ይህ በጎ ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም አመላክተዋል።
የልማት ቀበሌው አስተዳዳሪ አቶ ፍሬው ካሳሁን፤ ቡድኑ ለአካባቢው ወጣቶች አርአያ ከመሆን ባለፈ በቀበሌው በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ችግሮች ውስጥ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን እየደገፈ ይገኛል።
የእርሻ ጤና እግር ኳስ ቡድን ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ወንድማገኝ ታምሩ እና አለማየሁ አላሮ፤ ቡድኑ ከተቋቋመ ጀምሮ ጤናማና በስነ-ምግባር የታነፁ ወጣቶች እዲወጡ እያደረገና የተለያዩ በጎ ተግባራትንም እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል።
አንዳንድ ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች በተደረገላቸው ሰብዓዊ ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው ድጋፍን ላደረጉላቸው አካላትንም አመስግነዋል።
ዘጋቢ፡ እንጃ ገልሲሞ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
በከተማው የሚገኙ እግር ኳስ ቡድኖች ተወዳዳሪና ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚያደርጉት በጎ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የአርባምጭ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመረጃ ጥራት ዙሪያ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተጠቆመ
የሀገሪቱን የሥጋ ምርት ጥራትና መጠን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉ አቀፍ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ