የአርባምንጭ የድል ፋና የመጀሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን አንዳንድ በሆስፒታሉ ያገኘናቸዉ ተገልጋዮች ተናገሩ
አንዳንድ በሆስፒታሉ የሚታዪ የህክምና ቁሳቁሶች ጉድለት እንዲሟሉም ተገልጋዮቹ ጠይቀዋል።
አቶ ኃይሉ ዳንኤል ከኦሮሚያ ክልል ገላና ወረዳ ለህክምና የመጡ ሲሆን የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በሚሰጡት አገልግሎት መደሰታቸዉን ገልፀዉ አገልግሎት አሰጣጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱንም ተናግረዋል።
በሆስፒታሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አሰበች ዳኮማ እና አቶ አየለ ሆስፒታሉ አገልግሎት የሚሰጡ ባሉየዎች ከአቀባበል ጀምሮ በሚሰጠዉ አገልግሎት መርካታቸዉን ተናግረዋል።
በሆስፒታሉ የአጠቃላይ ሀክም ዶ/ር ይድንቃቸዉ ሳሙኤል ተገልጋዮች በሆስፒታሉ ተገቢዉን አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ሁሉም ባለሙያዎች በቅንነት እዲያገለግሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በሆስፒታሉ የሚስተዋሉ አንዳንድ የህክምና ቁሳቁሶችና የመድኃት እጥረት የበለጠ ተገልጋዮችን ለማርካት እንቅፋት መሆናቸዉንም ተናግረዋል።
የሆስፒታሉ ሜድካል ዳይሬክተር ዶ/ር መታሠቢያ መለሰ ተቋሙ ከጤና ጣቢያ ወደ ሆስፒታል ካደገ ጊዜ ጀምሮ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠቱ የተገልጋይ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።
ተገልጋዮችን የበለጠ ለማርካት የቀዶ ጥገና ክፍል እና ተጨማሪ አልጋ ያስልጋል ያሉት ዶ/ሩ ሆስፒታሉ የሚሰጠዉን አገልግሎት በማስፋት በቅርቡ ተጨማሪ የህክምና ቁሳቁሶች ወደ ሥራ እንደሚገቡ ገልፀዋል።
የሚስተዋለዉ የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ ከጋሞ ልማት ማህበር ጋር በመሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ዘጋቢ ፡ ካታንሾ ካርሶ

More Stories
በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል ድጋፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ሩዝ ያመረቱ አርሶ አደሮች ምርታማ መሆናቸውን ገለፁ
በክልሉ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ እናቶችና ሴቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናቸው እንዲጠበቅ በትኩረት መሠራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ
የነበሩ ችግሮች እየተቀረፉ በመምጣታቸው የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን በከምባታ ዞን አንዳንድ የዶዮገና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተገልጋዮች ተናገሩ