የጤና ሚኒስቴር 4.2 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው የህክምና መሣሪያዎች ለክልልና ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች ድጋፍ አደረገ
የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ስርአትን ለማጠናከር የሚያስችል የህክምና መሣሪያዎች ድጋፍ ጤና ሚኒስቴር ለክልል እና ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮዎች አድርጓል።
የህክምና መሣሪያዎች የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ ድርሻ አላቸው ናቸው ያሉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ የተደረገው ድጋፍ የጤና ተቋማት የህክምና መሣሪያዎች የረጅም ጊዜ ፍላጎትን የሚያሟላ መሆኑን ገልፀዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ በመቀጠልም የጤናው ዘርፍ ትልቁ ወጪ የህክምና መሣሪያዎች ግዢ መሆኑን በመግለፅ እያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን በተገቢዉ መልኩ ጥቅም ላይ እንዲያዉሉ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ በበኩላቸው፤ አዲሱ የመድሃኒት ግዢ አዋጅ የተሻለ የህክምና መሣሪያዎች ግዢ ስርዓት እንዲፈጠር በማድረጉ አገልግሎቱ በፍጥነት የህክምና መሣሪያዎች ማቅረብ እንዲችል አድርጎታል ብለዋል።
በድጋፉም ለ48 የጤና ጣቢያዎች ሙሉ ኪት፣ ለ162 አጠቃላይ ጤና ኬላዎች ኪት፣ ለ50 መሰረታዊ ጤና ኬላዎች ግብዓት፣ ለ14 ጤና ጣቢያዎች የቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጫ ሙሉ መሳሪያዎች(ኪት)፣ ለ60 የፅኑ ህክምና ማዕከል ግብዓት፣ 33 ዲጂታል X-Ray መሳሪያዎች፣ 19 የላውንደሪ ማሽን፣ 117 የአይን የህክምና መሳሪያዎች እና ከ3000 በላይ የደም ግፊት መመርመሪያ መሳሪያዎች ተካተዋል።
ከጤና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የክፍፍል ስርዓቱ በፍትሀዊነት ሁሉንም አካባቢ ተጠቃሚ እንዲያደርግ የታሰበ ሲሆን ድጋፉን የክልል እና የከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊዎች ተረክበዋል።
More Stories
የእናቶችንና ህጻናትን ሞት ለማስቀረት የቅድመ ማህጸን በር ካንሰርንና ከቅድመ ወሊድ እስከ ድህረ ወሊድ ያሉትን ምርመራዎች ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የአርባምንጭ ደምና ህብረህዋስ ባንክ በ2017 በጀት አመት ከ6 ሺህ 378 ዩኒት በላይ ደም መሰብሰብ መቻሉን አስታወቀ
ጤናማና ደህንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየተሰራ ነው – የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት