በጋሞ ዞን የዘፍኔ ከተማ አስተዳደርነት መዋቅር መፈቀዱ ለከተማ ዕድገት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ
የከተማው አስተዳደሩ በበኩሉ የህዝብ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፆ ህዝቡ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የልማት ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን የገለፁት የዘፍኔ ከተማ ነዋሪ አቶ መሸሻ ማዳ በተለይም አሁን ላይ የከተማ አስተዳደር መዋቅር ተፈቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ የልማት ጥያቄን ለመመለስ ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሯል ብለዋል።
አቶ ገረሱ ዳርጫ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ ሲሆኑ የከተማ አስተዳደር መፈቀዱና ወደ ሥራ መገባቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።
መምህርት ሰላምነሽ ሲሳይ በበኩላቸው ለሥራ አጥ ወጣቱ የሥራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።
የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መለሰ ማርካ ህብረተሰቡ አገልግሎት በቅርበት ማግኘት እንዲችል የከተማ አስተዳደር መዋቅር መፈቀዱ በዋናነትም የህዝብ ጥያቄ ፍትሐዊና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ ምላሽ እንዲያገኝ ያግዛል ሲሉ ተናግረዋል ።
በቀጣይ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ውጤታማ መሆን እንዲችሉ ህዝቡ ከአስተዳደሩ ጎን እንዲሆን ከንቲባው ጥሪ አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ታምሩ በልሁ ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እና ያለብክነት ሊሰበሰብ እንደሚገባ የባኮ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አሳሰበ