በጋሞ ዞን የዘፍኔ ከተማ አስተዳደርነት መዋቅር መፈቀዱ ለከተማ ዕድገት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ
የከተማው አስተዳደሩ በበኩሉ የህዝብ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፆ ህዝቡ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የልማት ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን የገለፁት የዘፍኔ ከተማ ነዋሪ አቶ መሸሻ ማዳ በተለይም አሁን ላይ የከተማ አስተዳደር መዋቅር ተፈቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ የልማት ጥያቄን ለመመለስ ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሯል ብለዋል።
አቶ ገረሱ ዳርጫ ሌላኛው የከተማው ነዋሪ ሲሆኑ የከተማ አስተዳደር መፈቀዱና ወደ ሥራ መገባቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።
መምህርት ሰላምነሽ ሲሳይ በበኩላቸው ለሥራ አጥ ወጣቱ የሥራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።
የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መለሰ ማርካ ህብረተሰቡ አገልግሎት በቅርበት ማግኘት እንዲችል የከተማ አስተዳደር መዋቅር መፈቀዱ በዋናነትም የህዝብ ጥያቄ ፍትሐዊና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ ምላሽ እንዲያገኝ ያግዛል ሲሉ ተናግረዋል ።
በቀጣይ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ውጤታማ መሆን እንዲችሉ ህዝቡ ከአስተዳደሩ ጎን እንዲሆን ከንቲባው ጥሪ አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ታምሩ በልሁ ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ
በሀገሪቱ ያለው 80 በመቶ ቡና ያረጀ በመሆኑ መታደስ እንደሚገባ ተጠቆመ