በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ከ36 ሚሊዬን ብር በላይ ወጪ የተሰራው የኡማ ባኬ መንገድ ተጠናቆ ተመረቀ
የመንገዱ መገንባት ለአከባቢው ማህበረስብ ያለው ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ መሆኑም ተመላክቷል ፡፡
በመርሐግብሩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የመንግስት ረዳት ተጠረና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ የመንገድ መሰረተ ልማት የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማቶችን ሊደግፍ በሚችል መልኩ ለማስፋፋት መንግስት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
የመንገድ መሠረተ ልማት ልማትን የሚያሳልጡ፣ እድገትን የሚፋጥኑ፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ ተስፋን የሚያለመልሙ ሊሆን እንደሚገባ ነው ያነሱት፡፡
በዞኑ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መኖራቸውን አመልክተው፤ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የዞኑ ህዝብ እንዲያግዝ ጠይቀዋል ፡፡
የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ልከባቢው ማህበረሰብ የመንገድ መሰረተ ልማት ሁሉን አቀፍና የዘመናት ጥያቄ ምላሽ ነው ብለዋል ፡፡
የአመያ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባሻ በላይነህ አከባቢው ሰፊ የግብርና ምርት ያለበት መሆኑን ጠቅሰው በአከባቢው ምቹ የገበያ ትስስር ለመፍጥር የመንገዱ መገንባት አውንታዊ ሚና ይጫወታል ነው ያሉት ፡፡
ኡማ -ባኬ -ዝጋ መንገድ 12 ኪ.ሜ በላይ ሲሆን 36 ሚለዬን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ፡፡
ዘጋቢ ፡ደረጀ ተፈራ -ከዋካ ቅርነጫፍ
More Stories
ግብር ለከተማው ብሎም ለሀገር ልማት ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመስጠት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን በንግድ ሥራ ላይ የተሠማሩ ግብር ከፋዮች ተናገሩ
ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ገለፀ
ገቢ ከራስ ለራስ የሚዉል በመሆኑ በቴክኖሎጂ በተደገፈ የአከፋፈል ስርዓት በአጭር ቀናት ከታቀደው በላይ ግብር መሰብሰብ እንደሚገባ ተገለጸ