በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሠማሩ የግል ባለሀብቶች ከመንግስት የተረኩቡትን ሀብት በተገቢው እንዲያለሙ ተጠየቀ
የኣሪ ዞን ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ “ኢንቨስትመንት ለላቀ ብልጽግና” በሚል መርህ በዞኑ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ የግል ባለሀብቶች እና ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የኣሪ ዞን ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፍቅረስላሰ ጀማል በመድረኩ እንደገለፁት፤ በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ 77 የግል ባለሀብቶች ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል እያንቀሳቀሱ ይገኛል።
በዞኑ ለኢንቨስትመንት ከተላለፉ መሬቶች 36 በመቶ ብቻ እየለማ እንዳለ ገልፀው፤ በዘርፉ የሚሰተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ዞኑ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢንቨስትመንት ለሀገር ግንባታና ብልጽግና ካለው የላቀ አስተዋጾ አንጻር በዞኑ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
በዞኑ ለኢንቨስትመንት በሚቀርቡ መሬቶች ላይ የሚሰተዋሉ የግንዛቤና አፈፃፀም ችግሮችን በዘላቅነት በመፍታት ዘርፉን ለማሳደግና የዞኑንም ጥቅም ለማሳደግ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አፀደ አይዛ፤ መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማዘመን የሪፎርም እና በርካታ የአሰራር ማሻሸያዎችን ማድረጉን አብራርተው፤ በተዋረድ ያሉ የመንግስት መዋቅሮችና በዘርፉ የተሰማሩ የግል ባለሀብቶች የተፈጠሮ ዕድሎችን መጠቀም አለባቸው ብለዋል።
ቢሮ ኃላፊዋ አክለው በዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት እንደሚሰራ አረጋግጠው፤ አልሚ የግል ባለሀብቱም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በዳዉሮ ዞን ታርጫ ከተማ የሚካሄዱ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ልማቶች አሁን ላይ ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ ገለጹ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በማር ምርት ዘርፍ 360 ሺህ ሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ አስታወቁ
በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ