በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ
የ1ሺ 4መቶ 46ኛውን የአረፋ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ከ5መቶ 70 ሺ በላይ በሆነ ወጪ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ ፡፡
በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ አስተዳደር ከወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የአደጋ ስጋትና ምግብ ዋስትና እንዲሁም ከወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ተቋም ጋር በመሆን የ1ሺ 4መቶ 46ኛውን የአረፋ በዓል ምክንያት በማድረግ ከሁሉም የወረዳው ቀበሌዎች ለተውጣጡ 2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን 5መቶ 70 ሺ 5መቶ ብር በሆነ ወጪ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡
የሳንኩራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ተሚማ ሙዴ መረዳዳት እና መደጋገፍ መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን ሞራላዊ ግዴታም ጭምር እንደሆነ አንስተው የመረዳዳት ባህሉና ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የማዕዱ ተጋሪዎች በበኩላቸው ለተደረገላቸው መልካም ተግባር ምስጋና አቅርበዋል ።
ምንጭ ፡ የሳንኩራ ወረዳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን
More Stories
በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ እየተሳተፉ የሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ስራ አጥነትን ለመቅረፍ እያደረጉት ያለውን ድጋፍ አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ አስታወቀ
“ባለፉት ሰባት ዓመታት የክልሉ ገቢ የመሠብሰብ አቅም ከ7 ቢሊዮን ብር ወደ 13 ቢሊዮን ብር አድጓል” – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ በበልግና በመኸር ወቅት የተከናወኑ የግብርና ስራዎች የተሻለ ውጤት መታየቱን የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ገለጹ