በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ
የ1ሺ 4መቶ 46ኛውን የአረፋ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ከ5መቶ 70 ሺ በላይ በሆነ ወጪ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ ፡፡
በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ አስተዳደር ከወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የአደጋ ስጋትና ምግብ ዋስትና እንዲሁም ከወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ተቋም ጋር በመሆን የ1ሺ 4መቶ 46ኛውን የአረፋ በዓል ምክንያት በማድረግ ከሁሉም የወረዳው ቀበሌዎች ለተውጣጡ 2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን 5መቶ 70 ሺ 5መቶ ብር በሆነ ወጪ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡
የሳንኩራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ተሚማ ሙዴ መረዳዳት እና መደጋገፍ መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን ሞራላዊ ግዴታም ጭምር እንደሆነ አንስተው የመረዳዳት ባህሉና ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የማዕዱ ተጋሪዎች በበኩላቸው ለተደረገላቸው መልካም ተግባር ምስጋና አቅርበዋል ።
ምንጭ ፡ የሳንኩራ ወረዳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመረጃ ጥራት ዙሪያ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተጠቆመ
የሀገሪቱን የሥጋ ምርት ጥራትና መጠን በላቀ ደረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉ አቀፍ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ