በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ባደዋቾ ክላስተር በ2017/18 በበልግ የእርሻ ወቅት በክላስተር የተዘራ የበቆሎ ማሳ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በተመራ ልኡክ የመስክ ምልከታ ተደረገ
በምልከታው ከበቆሎ ማሳ በተጨማሪ በአካባቢው የተከናወኑ የተቀናጀ የግበርና ሥራ እንቅስቃሴ በዞኑና በወረዳዎቹ አመራሮች እንዲሁም በባለሙያዎች ተጎብኝቷል።
በሀዲያ ዞን ምስራቅ ባደዋቾ ወረዳ በ2017/18 የምርት ዘመን በበልግ አርሻ ወቅት በዘር ከተሸፈነው 7 ሺህ 2 መቶ ሄክታር ማሳ ውስጥ 5 ሺህ 9 መቶ 86 ያህሉ በኩታ ገጠም የተዘራ መሆኑም ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ በወረዳው 99 ክላስተር ማሳ በዘር ከተሸፈነው የአቶቴና ሊቻ ክላስተሮች ምልከታ የተደረጉ ሲሆን ከሄክታር 60 ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ኤልያስ ኤርሶ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ወጣቱ ትዉልድ በግብርናዉ ዘርፍ ያሉ አማራጮችን ተጠቅሞ የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ
በከተማ ያለውን ህገወጥ የንግድ ስርዓት እና ኮንትሮባንድን በማስቀረት ህጋዊ ነጋዴዎችን የመደገፍ እና የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ተገለጸ