በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ባደዋቾ ክላስተር በ2017/18 በበልግ የእርሻ ወቅት በክላስተር የተዘራ የበቆሎ ማሳ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በተመራ ልኡክ የመስክ ምልከታ ተደረገ
በምልከታው ከበቆሎ ማሳ በተጨማሪ በአካባቢው የተከናወኑ የተቀናጀ የግበርና ሥራ እንቅስቃሴ በዞኑና በወረዳዎቹ አመራሮች እንዲሁም በባለሙያዎች ተጎብኝቷል።
በሀዲያ ዞን ምስራቅ ባደዋቾ ወረዳ በ2017/18 የምርት ዘመን በበልግ አርሻ ወቅት በዘር ከተሸፈነው 7 ሺህ 2 መቶ ሄክታር ማሳ ውስጥ 5 ሺህ 9 መቶ 86 ያህሉ በኩታ ገጠም የተዘራ መሆኑም ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ በወረዳው 99 ክላስተር ማሳ በዘር ከተሸፈነው የአቶቴና ሊቻ ክላስተሮች ምልከታ የተደረጉ ሲሆን ከሄክታር 60 ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ኤልያስ ኤርሶ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ
በክልሉ የሚከናውኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሊሆኑ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ገለፁ
የአፈርና ውሃ ጥበቃ በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ