በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ባደዋቾ ክላስተር በ2017/18 በበልግ የእርሻ ወቅት በክላስተር የተዘራ የበቆሎ ማሳ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በተመራ ልኡክ የመስክ ምልከታ ተደረገ
በምልከታው ከበቆሎ ማሳ በተጨማሪ በአካባቢው የተከናወኑ የተቀናጀ የግበርና ሥራ እንቅስቃሴ በዞኑና በወረዳዎቹ አመራሮች እንዲሁም በባለሙያዎች ተጎብኝቷል።
በሀዲያ ዞን ምስራቅ ባደዋቾ ወረዳ በ2017/18 የምርት ዘመን በበልግ አርሻ ወቅት በዘር ከተሸፈነው 7 ሺህ 2 መቶ ሄክታር ማሳ ውስጥ 5 ሺህ 9 መቶ 86 ያህሉ በኩታ ገጠም የተዘራ መሆኑም ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ በወረዳው 99 ክላስተር ማሳ በዘር ከተሸፈነው የአቶቴና ሊቻ ክላስተሮች ምልከታ የተደረጉ ሲሆን ከሄክታር 60 ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ኤልያስ ኤርሶ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በሆሣዕና ከተማ የሚገነቡ ሆቴሎች የከተማውን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ከተማው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያደርግ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) ገለፁ
በደቡብ ኦሞ ዞን በሣላማጎ ወረዳ በሌማት ትሩፋት በቆላማ አካባቢ የኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት ድጋፍ በዶሮ እርባታ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ
በጎፋ ዞን ከ950 ቶን በላይ የብረት ማዕድን ክምችት መኖሩ ተገለጸ