በክትባት ዘመቻው 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ህፃናትን ይከተባሉ-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ
ከግንቦት 22/2017ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ለሚካሄደው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ጠይቋል።
ከግንቦት 22 እስከ 25/2017ዓ.ም በሚካሄደው ዘመቻ 1ሚሊዮን 4መቶ ሺህ ህፃናትን ተደራሽ እንደምደረግ ቢሮው አስታወቀ።
በክልሉ ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ባይጽማል ቀበሌ ዞናዊ የማስጀመሪያ መረሐ ግብር ላይ ተገኝተው ክትባቱን በይፋ ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ኤች.አይ.ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍና ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ጋርሾ በበጀት አመቱ በክልሉ የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የተሳካ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል ፡፡
በክልሉ ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው ክትባት ዘመቻ ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ህፃናት ይከተባሉ ብለዋል ፡፡
ከፖሊዮ ክትባት ጎን ለጎን በወባ በሸታ መከላከያና ምልክቶች ላይ በተቀናጀ መንገድ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ያመላከቱት አቶ ማቴዎስ ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግና መከተብ ያለባቸውን ህፃናት በሙሉ እንዲያስከትቡ አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሁን ገሎ በማስጀመሪያው ባስተላለፉት መልዕክት
በዞኑ በተያዘው የሁለተኛ ዙር ክትባት ዘመቻ 77 ሺህ 3መቶ 6 ህፃናት ክትባት ያገኛሉ ነው ያሉት ፡፡
ዘጋቢ ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ-ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ እናቶችና ሴቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናቸው እንዲጠበቅ በትኩረት መሠራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ
የነበሩ ችግሮች እየተቀረፉ በመምጣታቸው የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን በከምባታ ዞን አንዳንድ የዶዮገና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተገልጋዮች ተናገሩ
የህብረተሰቡን የግልና አካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ባህል ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ