ማንቸስተር ሲቲ በኖቲንግሃም ፎረስት ተሸነፈ
በ28ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬርሊግ ሻምፒዮኑ ማንቸስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ በኖቲንግሃም ፎረስት 1ለ0 ተሸንፏል።
የኖቲንግሃም ፎረስትን የማሸነፊያ ግብ ሆድሶን ኦዶዬ በ83ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል።
ኖቲንግሃም ፎረስት ማንቸስተር ሲቲን ሲያሸንፍ ከ9 ጨዋታዎች በኋላ ነው።
ለመጨረሻ ጊዜ ሲቲዝኖቹን የረቱት እንደ አውሮፓውያኑ በ1997 ነበር።
በአሰልጣኝ ኑኖ ስፒሪቶ ሳንቶ የሚመራው ኖቲንግሃም ፎረስት ማሸነፉን ተክሎ ነጥቡን 51 በማድረስ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ማንቸስተር ሲቲ በአራት ነጥብ አንሶ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፕሪሚዬርሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከሳውዝሃምተን፣ብራይተን ከፉልሃም እንዲሁም ክርስቲያል ፓላስ ከኢፕሲች ታውን ይጫወታሉ።
ብሬንትፎርድ ከአስቶንቪላ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ሲጫወቱ ዎልቭስ ከኤቨርተን ደግሞ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የሚገናኙ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት