የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ
የቻይና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ይህ ድርጅት ኤም.ዲ.ኤፍና ኤች.ዲ.ኤፍ አምራችና 5.1 ቢሊዮን ካፒታል የሚያንቀሳቅስ ነው።
ፕሮጀክቱ 369 ቋሚና በግንባታ ሂደት ላይ ከ5000 በላይ ሰራተኞችን ይዟል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ካምፓኒው የውጭ ምርቶችን የሚተካ እንዲሁም ወደ ውጭ ምርቶችን የሚልክ ድርጅት ነው።
የግንባታ ሂደቱ አሁን ላይ ከ75 በመቶ በላይ የተጠናቀቀ ሲሆን በአመቱ መጨረሻ ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) እና የኢፌዲሪ ኢንዱስትሪ ሚንስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አሁናዊ የስራ እንቅስቃሴውን ተዟዙረው ጎብኝተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
በቀቤና ልዩ ወረዳ የሚገነቡት የኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል እና የፈትሁዲን ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተገለፀ