የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ
የቻይና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ይህ ድርጅት ኤም.ዲ.ኤፍና ኤች.ዲ.ኤፍ አምራችና 5.1 ቢሊዮን ካፒታል የሚያንቀሳቅስ ነው።
ፕሮጀክቱ 369 ቋሚና በግንባታ ሂደት ላይ ከ5000 በላይ ሰራተኞችን ይዟል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ካምፓኒው የውጭ ምርቶችን የሚተካ እንዲሁም ወደ ውጭ ምርቶችን የሚልክ ድርጅት ነው።
የግንባታ ሂደቱ አሁን ላይ ከ75 በመቶ በላይ የተጠናቀቀ ሲሆን በአመቱ መጨረሻ ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) እና የኢፌዲሪ ኢንዱስትሪ ሚንስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አሁናዊ የስራ እንቅስቃሴውን ተዟዙረው ጎብኝተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል