የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ
የቻይና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ይህ ድርጅት ኤም.ዲ.ኤፍና ኤች.ዲ.ኤፍ አምራችና 5.1 ቢሊዮን ካፒታል የሚያንቀሳቅስ ነው።
ፕሮጀክቱ 369 ቋሚና በግንባታ ሂደት ላይ ከ5000 በላይ ሰራተኞችን ይዟል።
የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የሆነው ካምፓኒው የውጭ ምርቶችን የሚተካ እንዲሁም ወደ ውጭ ምርቶችን የሚልክ ድርጅት ነው።
የግንባታ ሂደቱ አሁን ላይ ከ75 በመቶ በላይ የተጠናቀቀ ሲሆን በአመቱ መጨረሻ ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) እና የኢፌዲሪ ኢንዱስትሪ ሚንስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አሁናዊ የስራ እንቅስቃሴውን ተዟዙረው ጎብኝተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የመሠረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተገለጸ
በአከባቢዉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር እጥረት ችግር ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
የአከባቢን እና የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚቻለው ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት ማድረግ ሲቻል መሆኑ ተገለጸ