አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉይ መልቀቂያ አስገቡ
የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድነሰ ዋና አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉይ በገዛ ፈቃዳቸው ከሀላፊነት ለመነሳት መልቀቂያ ማስገባታቸው ተገልጿል።
አሰልጣኙ ላስገቡት የስራ መልቀቂያ የሞሮኮ እግርኳስ ፌዴሬሽን እስካሁን ምንም የገለፀው ነገር እንደሌለ ፉት መርካቶ አስነብቧል።
የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በፈረንጆቹ 2022 ነበር ብሔራዊ ቡድኑን በሀላፊነት የተረከቡት።
በቆይታቸውም ሞሮኮን በዓለም ዋንጫው ታሪክ ለግማሽ ፍፃሜ መድረስ የቻለች የመጀመሪያው አፍሪካዊት ሀገር እንድትሆን አስችለዋታል።
በተጨማሪም ከአንድ ወር በፊት በተጠናቀቀው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድኑን ከ21 ዓመታት በኋላ ለፍፃሜ ማብቃታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።