አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉይ መልቀቂያ አስገቡ
የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድነሰ ዋና አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉይ በገዛ ፈቃዳቸው ከሀላፊነት ለመነሳት መልቀቂያ ማስገባታቸው ተገልጿል።
አሰልጣኙ ላስገቡት የስራ መልቀቂያ የሞሮኮ እግርኳስ ፌዴሬሽን እስካሁን ምንም የገለፀው ነገር እንደሌለ ፉት መርካቶ አስነብቧል።
የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ በፈረንጆቹ 2022 ነበር ብሔራዊ ቡድኑን በሀላፊነት የተረከቡት።
በቆይታቸውም ሞሮኮን በዓለም ዋንጫው ታሪክ ለግማሽ ፍፃሜ መድረስ የቻለች የመጀመሪያው አፍሪካዊት ሀገር እንድትሆን አስችለዋታል።
በተጨማሪም ከአንድ ወር በፊት በተጠናቀቀው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድኑን ከ21 ዓመታት በኋላ ለፍፃሜ ማብቃታቸው ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሲዳማ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
ማንቸስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4ለ0 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፈ
አሌክሳንደር አይሳክ ወደ ልምምድ ሊመለስ ነው