ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን አሸነፈ

ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን አሸነፈ

በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን 2ለ0 አሸንፏል።

በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የማንቸስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ብሪያን ምቦማ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ አስገኝተዋል።

ማንቸስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

ቀያይ ሰይጣኖች ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 44 አድሰው 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ