ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን አሸነፈ
በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን 2ለ0 አሸንፏል።
በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የማንቸስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ብሪያን ምቦማ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ አስገኝተዋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።
ቀያይ ሰይጣኖች ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 44 አድሰው 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።