የቅርጫት ኳስ ሻምፒዮናው እንደቀጠለ ነው
ከፍተኛ ፉክክር እየተደረገበት የሚገኘው የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ስፖርት 3ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር የሴቶች ጨዋታዎች ዛሬ መቋጫውን አግኝቷል።
በትላንት ውሎ ሁለት ጨዋታን የተደረገ ሲሆን ወልቂጤ ከተማ ከባህርዳር ያገናኘው ጨዋታ በወልቂጤ ከተማ 56 ለ46 በሆነ ውጤት አሸናፊነት ተጠናቋል።
በሁለተኛው መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ ሲጫወቱ ሀዋሳ ከተማ 64 ለ47 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሶስተኛውን ዙር በድል ማጠናቀቅ ችሏል።
ውድድሩ ዛሬም በሶስት ጨዋታዎች የሚቀጥል ሲሆን በመጀመሪያው መርሀግብር ኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት አካዳሚ ከ ፋሲል ከተማ ጋር ረፋድ ላይ ይጫወታሉ።
የእለቱ ሁለተኛ መርሀግብር ሸገር ከተማ ከወልቂጤ ከተማ የሚያገናኝ ይሆናል።
የእለቱ የመጨረሻ መርሐግብር በጋምቤላ ከተማና በሀዋሳ ከተማ መካከል ቀን 6:00 ሰአት ላይ የሚደረግ ይሆናል።
ዘጋቢ : ዳዊት ዳበራ-ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል