ሀዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንድርታን በመርታት በሰፊ የግብ ልዩነት በመርታት ወደ አሸናፊነት ተመለሰ
በ21ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ ሀዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን 5ለ2 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል።
ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለሀዋሳ ከተማ የማሸነፊያ ግቦችን አሊ ሱሌማን 3 ጎሎችን በማስቆጠር ሀትሪክ መስራት ሲችል ቢንያም በላይ እና አቤኔዘር ዮሐንስ ቀሪ ግቦችን ከመረብ አሳርፈዋል።
መቀሌ 70 እንድርታን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ያሬድ ብርሐኑ በፍጹም ቅጣት እና ቦና አሊ አስቆጥረዋል።
አሊ ሱሌማን ዘንድሮ በፕሪሚዬርሊጉ ከባህርዳር ከተማው አጥቂ ወንድወሰን በለጠ በመቀጠል ሀትሪክ 2ኛው ተጫዋች ሆኗል።
ሀዋሳ ከተማን በድጋሚ በአሰልጣኝነት የተረከበው ሙሉጌታ ምህረት የመጀመሪያ የፕሪሚዬርሊግ ድሉን አስመዝግቧል።
ሀዋሳ ከተማ ማሸነፉን ተከትሎ በ19 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
3ኛ ተከታታይ ሽንፈቱን ያስተናገደው መቀሌ 70 እንድርታ በበኩሉ በ22 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ዘጋቢ፡ በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል