የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ መጠንም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ6 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ማደጉን የቦርዱ ሊቀመንበር አምባሳደር ዓለማየሁ ሰዋገኝ ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የባንኩን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በ32 ነጥብ 8 በመቶ ከፍ በማድረግ 27 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር እንዳደረሰው ተነግሯል።
ከዚህ ውስጥ የቁጠባ ሂሳብ ተቀማጭ 77 ነጥብ 8 በመቶ የሚሆነውን ከፍተኛ ድርሻ እንደያዘ ነው ባንኩ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መረጃ የተመላከተው።
ባንኩ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትና በሀገሪቱ ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር በአገር ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ያሳደሩትን መቀዛቀዝ ተቋቁሞ በአትራፊነት መቀጠል ስለመቻሉም ተገልጿል፡፡
ይህም ለባንኩ ባለአክሲዮኖችና ለአጠቃላይ ሰራተኞቹ የሚያበረታታ ውጤት ነው ተብሏል።
More Stories
በጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ በፍራፍሬ ችግኝ ተከላ ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ
በጎፋ ዞን በቀጣይ 6 ወራት የሚተገበር የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የሚያስችል ዕቅድ ዙሪያ ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል
በኮንትራት እና በአርሶ አደሩ የሚመረቱ ምርቶች ተበረታተዉ ለዉጭ ገበያ እንዲቀርቡ ማስቻል እንደሚገባ ተጠቆመ