የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ መጠንም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ6 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ማደጉን የቦርዱ ሊቀመንበር አምባሳደር ዓለማየሁ ሰዋገኝ ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የባንኩን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በ32 ነጥብ 8 በመቶ ከፍ በማድረግ 27 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር እንዳደረሰው ተነግሯል።
ከዚህ ውስጥ የቁጠባ ሂሳብ ተቀማጭ 77 ነጥብ 8 በመቶ የሚሆነውን ከፍተኛ ድርሻ እንደያዘ ነው ባንኩ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መረጃ የተመላከተው።
ባንኩ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትና በሀገሪቱ ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር በአገር ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ያሳደሩትን መቀዛቀዝ ተቋቁሞ በአትራፊነት መቀጠል ስለመቻሉም ተገልጿል፡፡
ይህም ለባንኩ ባለአክሲዮኖችና ለአጠቃላይ ሰራተኞቹ የሚያበረታታ ውጤት ነው ተብሏል።

More Stories
በኢንተርፕራይዝና ኢንቨስትመንት የልማት ስራዎች ላይ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገለጸ
በግብርናው ኢኮኖሚ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ ያለውን የእንስሳት ሀብት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሠራ ነው – የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር መሠረት አበራ
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን ግብርና መምሪያ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት አሰታወቀ