የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ መጠንም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ6 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ማደጉን የቦርዱ ሊቀመንበር አምባሳደር ዓለማየሁ ሰዋገኝ ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የባንኩን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በ32 ነጥብ 8 በመቶ ከፍ በማድረግ 27 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር እንዳደረሰው ተነግሯል።
ከዚህ ውስጥ የቁጠባ ሂሳብ ተቀማጭ 77 ነጥብ 8 በመቶ የሚሆነውን ከፍተኛ ድርሻ እንደያዘ ነው ባንኩ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መረጃ የተመላከተው።
ባንኩ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትና በሀገሪቱ ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር በአገር ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ያሳደሩትን መቀዛቀዝ ተቋቁሞ በአትራፊነት መቀጠል ስለመቻሉም ተገልጿል፡፡
ይህም ለባንኩ ባለአክሲዮኖችና ለአጠቃላይ ሰራተኞቹ የሚያበረታታ ውጤት ነው ተብሏል።
More Stories
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ግብዓቶች አጠቃቀም ማሻሻልና ማዘመን እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ጥራት ያለው ኮረሪማ ለገበያ ለማቅረብና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት መደረጉን የአሪ ዞን ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የቡና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ