ማንቸስተር ሲቲ ኒውካስልን 4ለ0 አሸነፈ
በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬርሊግ ማንቸስተር ሲቲ ኒውካስል ዩናይትድን 4ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
ለማንቸስተር ሲቲ የማሸነፊያ ግቦችን ኦማር ማርሙሽ በ14ኛው፣24ኛው እና 33ኛው ደቂቃ ላይ በማስቆጠር ሀትሪክ መስራት ሲችል ቀሪዋን ግብ ተቀይሮ የገባው ጀምስ ማካቴ በ84ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል።
በማንቸስተር ሲቲ የመጀመሪያ ጎሎችን በ14 ደቂቃዎች ማስቆጠር የቻለው ማርሙሽ በእግር ኳስ ተጫዋችነት ዘመኑም የመጀመሪያ ሃትሪኩን ነው የሰራው።
ማንቸስተር ሲቲ በኤቲሀድ ስታዲየም ኒውካስልን በፕሪሚዬርሊጉ ለ16ኛ ተከታታይ ጊዜ ረቷል።
ማግፓይሶች ላለፉት 25 ዓመታት ሲቲዝኖችን ከሜዳቸው ውጪ ማሸነፍ አልቻሉም።
ማንቸስተር ሲቲ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 24 በማድረስ 4ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ኒውካስል በ41 ነጥብ ወደ 7ኛ ደረጃ ተንሸራቷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ፉልሃም ኖቲንግሃም ፎረስትን 2ለ1፣ቦርንማውዝ ሳውዝሃምተንን 3ለ1፣ብሬንትፎርድ ዌስትሃምን 1ለ0 አሸንፈዋል።
አስቶንቪላ እና ኢፕሲች ታውን ያደረጉት ጨዋታ ደግሞ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።
ፕሪሚዬርሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ክርስቲያል ከኤቨርተን ይጫወታሉ።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል