ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሴክቶሪያል ጉባኤ ተካሂዷል።
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፤ የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት የሚቻለው ትክክለኛ የፍትህ ስርዓት ማስፈን ሲቻል ነው ብለዋል።
የዜጎችን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በተለይም የፍትህ ተቋማት በህዝቡ ዘንድ አመኔታ መፍጠር የሚችሉ ትክክለኛ ፍትህ ለማረጋገጥ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዜጎች የህግ የበላይነትን ጠንቅቀው እንዲያውቁ ከፍትህ ተቋማት በኩል የተጠናከረ ሥራ መሰራት አለበት ያሉት ዋና አስተዳዳሪ፤ ህብረተሰቡ ወንጀልን ቀድሞ ከመከላከል አኳያ የግንዛቤ ሥራዎች ላይ መሰራት አለበት ብለዋል።
በዞኑ የህዝቡን ሠላም ለመጠበቅና የተሻለ የፍትህ ሥርዓት በመዘርጋት የዜጎችን ጥያቄ ለመመለስ በተደረገው ጥረት ባለፉት ስድስት ወራት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመዋል።
ህዝቡን በፍትህ አገልግሎት ለማርካት የፍትህ ሥርዓት የማዘመን ስራ በቁርጠኝነት መሰራት አለበት በማለት በየደረጃው ያሉ የፍትህ ተቋማትም ሀላፊነታቸውን በትጋት መወጣት አለባቸው ብለዋል።
የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋው ስምኦን በዞኑ የህብረተሰቡን ፍትህ ጥያቄዎችን ለመመለስ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በቀጣይም ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና እንደጉድለት የታዩ ክፍተቶችን ለማረም በቅንጅት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ